Bookmark this item
£17.08
Free UK Delivery
Available - Usually dispatched within 4 days
Available - Usually dispatched within 4 days

Bookmark this item
የቅዱሳን ዘመን ስንል ምን ማለታችን ነው?
በጌታ በኢየሱስ ክርስቶር ሞት ተዋጅተን በትንሣኤው ዳግም የተወለድን ሁላችን፣ አምነን የዳንን አማኞች ብቻ ሳንሆን ቅዱሳን ለመሆን ተጠርተናል (ሮሜ 1፡7 ፥ 1ቆሮ 1፡2)። ቅዱሳን ማለት ለጌታ ለራሱ የተለዩ ገንዘቡ የሆነ ሕዝብ ማለት ነው (ቲቶ 2፡14)። ቅዱሳንነት ጥሪ እንጂ ስም አይደለም። ይህም ጥሪ ለጥቂቶች ብቻ የተሰጠ ሳይሆን፣ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅነት ላመኑ ሁሉ የተሰጠ ጥሪ ነው። ቅዱሳን ለመሆን እንደተጠራን የነገረን የእግዚአብሔር ቃል፣ መጠራት ብቻ ሳይሆን በተጠራንበትም መጠራት መመላለስ እንዳለብንም ያሳስበናል (ኤፌ 4፡1)። ስለዚህም ነው ቅዱሳን የሚለው ቃል መጠሪያ ብቻ ያልሆነው።
ስለዚህ የቅዱሳን ዘመን ብለን ስንናገር፣ በቅድሚያ፣ ያመንን ሁሉ፣ ቅዱሳን (የተለዩ) ለመሆን ሁላችን እንደተጠራን እውቀቱ እንዲኖረንና በተጨማሪም በተጠራንበት መጠራት መመላለስ ደግሞ ሁላችን እንደሚጠበቅብን ግንዛቤ ውስጥ እንድናስገባም ነው። እነዚህን ሁለት ነገሮች መረዳትና በእነዚህ መረዳቶችም መመላለስ የቅዱሳንን ዘመን ማምጣት ብቻ ሳይሆን፣ የቅዱሳን ዘመን መምጣት አብሳሪዎች እንድንሆንም ያነቃቃል።
ይህ የመጀመርያ ቅጽ በሦስት ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን፣ የመጀመርያው ክፍል የእግዚአብሔርን ቅዱስነት በተመለከተ የሚናገር ነው። ስለ ቅዱሳን ከመናገራችን በፊት የእግዚአብሔርን ቅዱስነት ማየትና መመልከት አስፈላጊ ነው። በሁለተኛው ክፍል ስለ ቅዱሳን ወይም ስለ ቅዱስ ሕዝብ እንመለከታለን። ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር ነው ቅዱስ ሕዝብ ሊኖረው የሚችለው። እንዲሁም በመጨረሻው ክፍል ላይ በተለያየ ዘመን እግዚአብሔር የተለያየ የሥራ ትኩረት ሊኖረው ስለሚችል አሁን ያለው የሥራ ትኩረት ለማየት ዘመኑን ስለማወቅ እንመለከታለን። ዘመኑን ካላወቅን አሁን ያለንበትን ዘመን የቅዱሳን ዘመን ነው ልንል አንችልም። መልካም ንባብ
Title
Saints Era - Volume 1
Author
Ermias Tilahun
Book Format
Paperback / softback
Publisher
Indy Pub
Published
September 2018
Weight
287g
Dimensions
15.3 x 22.9 x 1.2 cm
ISBN
9781087922379
ISBN-10
1087922372
Eden Code
5508573
For you
Free delivery on orders over £15
£17.08
Free UK Delivery
Available - Usually dispatched within 4 days
Available - Usually dispatched within 4 days
